የባልደራስ የቀድሞው መሪ እስክንድር ነጋ ከእስር መለቀቅ

Your browser doesn’t support HTML5

የባልደራስ የቀድሞው መሪ እስክንድር ነጋ ከእስር መለቀቅ

በቅርቡ ራሳቸውን ከፖለቲካ ማግለላቸውን የገለጹት አቶ እስክንድር ነጋ ከሁለት ቀናት እስር በኋላ በትናንትናው ዕለት ተለቀዋል።

የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ መስራች እና የፓርቲው ፕሬዝዳንት የነበሩት አቶ እስክንድር ነጋ የካቲት 17/2015 ዓ.ም አመሻሽ ላይ በምዕራብ ጎጃም ዞን ቡሬ ወረዳ አካባቢ በፀጥታ ኃይሎች ተይዘው ከቆዩ በኋላ ትላንት መለቀቃቸውን ፓርቲው አስታውቋል፡፡

ጉዳዩን በተመለከተ አስተያየታቸውን የጠየቅናቸው የፓርቲው ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ቀለብ የቀድሞው የባልደራስ መሪ “በቁጥጥር ስር የዋሉት ምንም አይነት የእስር ማዘዣ ሳይወጣባቸው እና የተለቀቁትም ለፍርድም ሳይቀርቡ ነው” ያሉት ወ/ሮ ቀለብ፣ ተጨማሪ አስተያየት ከመስጠት ግን ተቆጥበዋል፡፡

ስለ አቶ እስክንድር እስርም ሆነ ከእስር የመለቀቃቸው ጉዳይ በመንግሥት በኩል እስካሁን የተባለ ነገር የለም፡፡

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ፡፡