ደራሼ ውስጥ ዳግም በተቀሰቀሰ ግጭት ሁለት ሰው ተገደለ

Your browser doesn’t support HTML5

ደራሼ ውስጥ ዳግም በተቀሰቀሰ ግጭት ሁለት ሰው ተገደለ

በደቡብ ክልል መንግሥት መደበኛ ፖሊሶችና እና በደራሼ ልዩ ወረዳ ነዋሪዎች መካከል በተቀሰቀሰ ግጭት ሁለት ሰው መገደሉን በቦታው ነበርን ያሉ ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምጽ ተናገሩ። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አንድ የፖሊስ አባል እና በወንጀል ይፈለግ ነበር ያሉት አንድ ግለሰብ መገደላቸውን ገልጸው፤ “ችግሩ የተፈጠረው በወንጀል ተጠርጥረው የሚፈለጉ ሰዎችን ለማስመለጥ የፈለጉ ቡድኖች በፈጠሩት ሁከት ነው” ብለዋል።