የአሜሪካ ዲሞክራሲ ፈተና በአጋማሽ ምርጫ

Your browser doesn’t support HTML5

የአሜሪካ ዲሞክራሲ ፈተና በአጋማሽ ምርጫ

ዛሬ በዩናይትድ ስቴትስ እየተካሄደ ከሚገኘው የአጋማሽ ዘመን የምክር ቤት እና የአካባቢ ምርጫ አንድ ሳምንት ቀደም ብሎ፣ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ለሕዝባቸው ባደረጉት ንግግር "የአሜሪካ ዲሞክራሲ ጥቃት እየደረሰበት ነው" ብለው ነበር።

ለዚህም ከርሳቸው በፊት ፕሬዚዳንት የነበሩት ዶናልድ ትረምፕ የምርጫ ውጤቱን ለመቀበል ፈቃደኛ አለመሆናቸውን እንደምክንያትነት ጠቅሰዋል።

በአሜሪካ ምክር ቤት ላይ የደረሰውን የጥር 6 ጥቃት እና ከሳምንታት በፊት በም/ቤቱ አፈጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ ባለቤት ላይ የተፈፀመውን ጥቃት በመጥቀስም የፖለቲካ ሁከት እየጨምረ መሄዱን አመልክተዋል።

ሆኖም አንዳንድ ተንታኞች በአሜሪካ የዲሞክራሲ ማሽቆልቆል የጀመረው ከትረምፕ በፊትም እንደሆነ በመግለፅ ይከራከራሉ። ለመሆኑ የአሜሪካ ዲሞክራሲ የተደቀኑበት ፈተናዎች ምንድን ናቸው?

በሞርጋን ስቴት ዩኒቨርስቲ መምህር የሆኑትን ፕሮፌሰር ጌታቸው መታፈሪያ ማብራሪያ ሰጥተውናል።

/ሙሉውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/