የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተቋርጦባቸው የነበሩ የአላማጣ ከተማና አካባቢው አገልግሎቱን ማግኘት ጀመሩ

Your browser doesn’t support HTML5

የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተቋርጦባቸው የነበሩ የአላማጣ ከተማና አካባቢው አገልግሎቱን ማግኘት ጀመሩ

በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተቋርጦባቸው ከቆዩት አካባቢዎች መካከል የአላማጣ ከተማና አካባቢው ቀበሌዎች ከትናንት ጀምረው አገልግሎት ማግኘታቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡ ሌሎች የአማራና የትግራይ ክልል ከተሞችም አገልግሎቱን የሚያገኙበት ሁኔታ መፈጠሩን አመልክቷል።

በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት ጉዳት ደርሰበት የነበረው የወልዲያ አላማጣ ከፍተኛ የኃይል ማስተላላፊያ መስመር ተጠግኖ ኃይል ለማከፋፈል የሚያገለግለው መስመር ዝግጁ መሆኑን ተቋሙ ጠቅሷል።

[ሙሉውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ያገኛሉ]