ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መውጫ ፈተና ሊሰጥ ነው

  • ቪኦኤ ዜና

Your browser doesn’t support HTML5

ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መውጫ ፈተና ሊሰጥ ነው

በኢትዮጵያ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የሚደረገው ጥረት መቀጠሉን የገለፀው የትምህርት ሚኒስቴር ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ለዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና እንደሚሰጥ አስታውቋል፡፡

የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል ሌሎች የተለያዩ ጥረቶች እንደሚደረጉም የትምሀርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ተናግረዋል፡፡

የመውጫ ፈተና መስጠት፣ ተመራቂዎች በሚቀጠሩበት ጊዜ ፍትሀዊ ውድድር እንዲያደርጉ ያግዛል፣ ተቀራራቢ ብቃት እንዲኖራቸውም ያስችላል ይላሉ ምሁራን፡፡

ሆኖም፣ እርምጃው የራሱ የሆኑ ችግሮች እንደሚኖሩት ምሁራኑ ለአሜሪካ ድምፅ ገልፀዋል፡፡

[ሙሉውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ያገኛሉ]