በአለምዋጭ መጠለያ ጣቢያ ያሉት ኤርትራውያን ስደተኞች ጉዳይ

Your browser doesn’t support HTML5

በአለምዋጭ መጠለያ ጣቢያ ያሉት ኤርትራውያን ስደተኞች ጉዳይ

በሰሜን ጎንደር፣ ዳባት ወረዳ አለምዋጭ መጠለያ ጣቢያ ውስጥ የሚገኙ የኤርትራ ስደተኞች የምግብ አቅርቦትና የመሰረታዊ አገልግሎቶች እጥረት እንዳለባቸው ገለፁ፡፡

የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን ዩኤንኤችሲአር በኢሜል በሰጠው ምላሽ የሰብዓዊ ድርጅቶችን ያጋጠማቸው የገንዘብ እጥረት ተጽእኖ ማሳደሩን ጠቁሟል።

በዚህም ምክንያት ለስደተኞች የሚቀርበው የምግብ መጠን በግማሽ ቀንሷል ብሏል።

የዓለም ምግብ ፕሮግራም፣ የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ኮሚሽን እና የኢትዮጵያ ስደተኞችና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት ከሳምንታት በፊት በጋራ ባወጡት መግለጫም በኢትዮጵያ ውስጥ ለሚኖሩ 750 ሺህ ስደተኞች ሰብአዊ ድጋፍ ለማቅረብ 73 ሚሊዮን ዶላር ያስፈልጋል ሲሉ አስታውቀዋል።

[ሙሉውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ያገኛሉ]