የሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ተፈናቃዮች አሁንም ዕርዳታ እየጠበቁ ነው

የኢትዮጵያ ካርታ

እስካሁን የሰብዓዊ ድጋፍ እንዳልተደረገላቸው ከነሐሴ 23 እስከ ነሐሴ 25 በተፈፀመው ጥቃት ከሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን፣ አሙሩ ወረዳ የተፈናቀሉ ዜጎች ተናግረዋል ።

በታጣቂዎች በተፈጸመው ጥቃት ምክንያት ከአጋምሳ ከተማ እና አጎራባች ወረዳዎች የተፈናቀሉት እነዚህ ዜጎች በትምህርት ቤቶች እና በዕምነት ተቋማት ተጠልለው እንደሚገኙም ነው የገለፁት።

የሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን የአደጋ ስጋት ቅነሳ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በበኩሉ የተፈናቀሉ ሰዎችን መረጃ ለመሰብሰብ የተዋቀረ ኮሚቴ ወደ አካባቢው ማምራቱን አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ጷጉሜ 1/2014 ባወጣው መግለጫ ከ20 ሺህ በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውን ገልጾ፣ በአፋጣኝ ዕርዳታ እንዲደረግላቸውም አሳስቦ ነበር።

[ሙሉውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ያገኛሉ]

Your browser doesn’t support HTML5

የሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ተፈናቃዮች አሁንም ዕርዳታ እየጠበቁ ነው