የመብቶች ኮሚሽኑ በትግራይ ተፈናቃዮች ላይ

Your browser doesn’t support HTML5

የመብቶች ኮሚሽኑ በትግራይ ተፈናቃዮች ላይ

በአማራ ክልል ወሎ አካባቢ በጃራና ጃሬ ካምፖች ውስጥ ባለው የትግራይ ተፈናቃዮች የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ ላይ ምርመራ እያደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን አስታወቀ።

ኮሚሽኑ ባወጣው መግለጫ በአፋር ክልል በሰመራና አጋቲና ካምፖች ውስጥም ላለፉት ስምንት ወራት ተይዘው የቆዩ የትግራይ ተወላጆችን ወደየመኖሪያ አካባቢያቸው መመለስ መጀመሩንም አድንቋል።

በኮሚሽኑ የአፋር ክልል የሰብአዊ መብቶች ክትትልና ምርመራ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ግርማይ የኮሚሽኑን መግለጫ አስመልክተው ለቪኦኤ በሰጡት ማብራሪያ በሰዎቹ አያያዝ ላይ የሚደረገው ክትትል እንደቀጠለ መሆኑን፣ የተመለሱት ቁጥርም በመጨረሻው የክትትል ሪፖርት እንደሚገለፅ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን 9 ሺህ እንደሚሆኑ የገመታቸው፤ የአፋር ክልል ደግሞ 7 ሺህ 800 ናቸው የሚላቸው የትግራይ ተወላጆች መመለስ የጀመሩት በዚህ ሣምንት ነው።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።