የጨው እጥረት በኢትዮጵያ

Your browser doesn’t support HTML5

የጨው እጥረት በኢትዮጵያ

ኢትዮጵያ ውስጥ ከፍተኛ የጨው ምርት ክምችት ቢኖርም ገበያው ላይ እጥረት መፈጠሩን ነጋዴዎችና ተጠቃሚዎች ይናገራሉ።

በአፋር ክልል ከፍተኛ የጨው ምርት ክምችት መኖሩም የገለፀው የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር በክልሉ አፍዴራ ላይ ብቻ 40 ሚሊዮን ኩንታል ጨው ተመርቶ ወደገበያ አለመግባቱን አረጋግጧል፡፡

መንግስት በደለደለላቸው ኮታ መሰረተ ምርታቸውን ለመግዛት ውል የገባው ድርጅት ቃሉን ባለማክበሩ ለኪስራ ጭምር መዳረጋቸውን ጨው አምራቾቹ ይናገራሉ።

ጨው ላይ አዮዲን ጨምረው፣ ፈጭተውና በመጠን አሽገው ለሸማቹ የሚያቀርቡ ፋብሪካዎችም ደግሞ በጨው እጥረት ምክንያት ስራ ማቆማቸውን ለአሜሪካ ድምጽ ገልጸዋል፡፡

በምርት እጥረቱ ምክንያት ግለሰብ ሸማቾች ከ3 እስከ አምስት ብር የሚገዙትን አንድ ኪሎ ጨው እስከ 40 ብር አውጥተው ለመሸመት መገደዳቸውን ያስታወቁ ሲሆን ጨውን በግብአትነት የሚጠቀሙ ኢንዱስትሪዎችም የችግሩ ሰለባ እየሆኑ ነው ተብሏል፡፡

/ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/