ልጃቸውን እና ንብረታቸውን በጎርፍ የተነጠቁ ቤተሰቦች

Your browser doesn’t support HTML5

ልጃቸውን እና ንብረታቸውን በጎርፍ የተነጠቁ ቤተሰቦች

በአዲስ አበባ ከተማ እየጣለ ያለው ከባድ ዝናብ የሚያስከትለው ጎርፍ እንደወትሮው ሁሉ በሕይወትና በንብረት ላይ ጉዳት እያደረሰ ነው።

ባለፈው እሁድ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አማኑኤል ሆስፒታል አካባቢ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ የሌሎችን ሕይወት ለማዳን ሲጥር የነበረ አንድ ታዳጊ ወጣት ሕይወት አልፏል፡፡

የሟቹን ቤተሰቦች ጨምሮ ንብረታቸውን በሙሉ ያጡ የአደጋው ተጎጂዎች ለችግር መጋለጣቸውን ገልፀዋል።

በክረምቱ የጎርፍ አደጋ የሁለት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ለቪኦኤ የገለጸው የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ለተጎጂዎች ስለሚደረገው ድጋፍ ለተነሳለት ጥያቄም ምላሽ ሰጥቷል፡፡

/ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/