ሱዳን እና ኢትዮጵያ በንግድ የሚያገናኘው መንገድ ተከፈተ

በግጭት ምክኒያት ለ25 ቀናት ዝግ ሆኖ የቆየው ሱዳን እና ኢትዮጵያ በንግድ የሚያገናኘው ገላባት መተማ ዩሃንስ መንገድ ዛሬ መከፈቱን የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ እና የአካባቢው ነዋሪዎች ገለፁ።

የሱዳን መንግሥት መንገዱን ከሦስት ቀናት በፊት መክፈቱን ማስታወቁን የገለፁት የምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳዳሪ ቢክስ ወርቄ በኢትዮጵያ በኩል ደግሞ ዛሬ መከፈቱን ተናግረዋል።

የመንገዱ መከፈት በሁለቱ ሀገራት መሃከል ያለውን ሰላማዊ ግንኙነት እንደሚያጠናክር እና ለንግድ እንቅስቃሴውም ጠቃሚ መሆኑን ተናግረዋል።

/ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/

Your browser doesn’t support HTML5

ሱዳን እና ኢትዮጵያ በንግድ የሚያገናኘው መንገድ ተከፈተ