በጋምቤላ የሰዓት እላፊ ገደብ ተጣለ

Your browser doesn’t support HTML5

በጋምቤላ የሰዓት እላፊ ገደብ ተጣለ

በጋምቤላ ክልል ጋምቤላ ከተማ የሰዓት እላፊ ገደብ መጣሉን የክልሉ መንግሥት ኮምኒኬሽንስ ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

የሰዓት ዕላፊው ከምሽቱ ሁለት ሰዓት እስከ ንጋቱ 11 ሰዓት ተኩል መሆኑን የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ኡገቱ አዲንግ ተናግረዋል።

ገደቡ አምቡላንስን እና የመንግሥት ጸጥታ ኃይሎች ተሽከርካሪዎችን እንደማያካትት አስታውቀዋል።

/ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/