የሚድያ ባለሙያዎቹ የዋስትና ውሣኔ ተሻረ

Your browser doesn’t support HTML5

የሚድያ ባለሙያዎቹ የዋስትና ውሣኔ ተሻረ

ሦስቱ የሚዲያ ባለሙያዎች ተመስገን ደሳለኝ፣ ሰሎሞን ሹምዬና መዓዛ መሐመድ በአሥር ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቁ ተላልፎ የነበረውን ውሣኔ ፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዛሬ ሽሮታል።

ችሎቱ ለፖሊስ የስምንት ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ፈቅዷል።

በተያያዘ ዜና በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የጊዜ ቀጠሮ ችሎት የቀረበው “አልፋ ቴሌቪዥን” የሚባል የዩትዩብ ሚዲያ አዘጋጅ በቃሉ አላምረው የቀረበበት ክስ መታየት ያለበት በብሮድካስት አዋጅ አለያም በጊዜ ቀጠሮ በሚለው ጉዳይ ላይ ብይን ለመስጠት ለነገ መቀጠሩን ጠበቃው ገልፀዋል።

ዘገባው የኬኔዲ አባተ ነው።