በስደት ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያዊቷ ጋዜጠኛ

Your browser doesn’t support HTML5

በስደት ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያዊቷ ጋዜጠኛ

የአሜሪካ ድምፅ ዓመታዊውን የፕሬስ ነፃነት ቀን በማስመልከት ከትውልድ አገራቸው ተሰደው በውጭ የሚገኙ ጋዜጠኞች አነጋግሯል።

ድምበር የለሹ የጋዜጠኞች ቡድን እንደ አውሮፓውያን የቀን አቆጣጠር በ2021 ባወጣው ሪፖርት በዓለም ዙሪያ 488 ጋዜጠኞች ለእስር መዳረጋቸውን ጠቅሶ ከእነዚህ ውስጥ 60ዎቹ ሴቶች መሆናቸውን አስታውቆ ነበር።

በተቋሙ ጥናት መሰረት ለእስር የሚዳረጉ ሴት ጋዜጠኞች ቁጥር ባለፈው ዓመት ከነበረው በ33 ከመቶ ጨምሯል። በኢትዮጵያ መንግሥት የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ለእስር ተዳርገው ከነበሩ ሴት ጋዜጠኞች መካከል ርዕዮት አለሙ አንዷ ስትሆን ስመኝሽ የቆየ ርዕዮት በአምስት ዓመት የእስር ቆይታዋ የደረሰባት የስቃይ ምርመራና ማስፈራራት ስላሳደረባት ተፅእኖ እና ከሀገር ከወጣች በኃላ ጋዜጠኛ ሆኖ መሥራት ምን እንደሚመስል አነጋግራታለች።

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ያዳምጡ።