አዲሱ የአሜሪካ ልዑክ አዲስ አበባ ናቸው

  • መለስካቸው አምሃ

Your browser doesn’t support HTML5

አዲሱ የአሜሪካ ልዑክ አዲስ አበባ ናቸው

የዩናይትድ ስቴትስ ረዳት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና አዲሱ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ዛሬ ከኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር አዲስ አበባ ላይ እንደሚነጋገሩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ጠቁመዋል።

35ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ በመጭው ሣምንት አዲስ አበባ ውስጥ መካሄድ መቻሉ ለኢትዮጵያ ትልቅ ዲፕሎማሲያዊ ድል እንደሆነ ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

የአፍሪካ መሪዎች አዲስ አበባ ላይ ለመገናኘት መወሰን “ሰላም የለም” የሚለውን ንትርክ ያፈርሳል” ብለዋል ዲና ሙፍቲ።