አብአላ ላይ በተፈፀመ ጥቃት ህይወት ጠፍቷል፤ ብዙ ተፈናቅሏል

የህወሓት ታጣቂዎች ያደርሷቸዋል ባሏቸው የከባድ መሣሪያ ጥቃቶች በአፋርና በትግራይ አዋሳኝ ላይ በምትገኘው አብአላ ከተማ ብዙ ሰው መገደሉንና በሺሆች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን የአፋር ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።

በሌላ በኩል ከተማዪቱ ላይ “የፌደራል መንግሥቱ ደጋፊዎች አድርሰዋል” ባሉት ድብደባ “ከ250 በላይ የትግራይ ተወላጆች ተገድለዋል፤ ከ900 በላይ ተፈናቅለዋል” ሲል ህወሓት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

አብአላ ለትግራይ እርዳታ በየብስ በሚተላለፍበት የሰመራ-አብአላ-መቀሌ መስመር (ኮሪዶር) ከተማ ነች።

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

አብአላ ላይ በተፈፀመ ጥቃት ህይወት ጠፍቷል፤ ብዙ ተፈናቅሏል