ሃይቅ ውስጥ “በትንሹ 48 ሲቪሎች ተገድለዋል” - አስተዳደሩ

Your browser doesn’t support HTML5

ሃይቅ ውስጥ “በትንሹ 48 ሲቪሎች ተገድለዋል” - አስተዳደሩ

ሐይቅ ከተማ ውስጥ “በትንሹ 48 ሲቪሎች በህወሓት ታጣቂዎች ተገድለዋል” ሲል የከተማ አስተዳደሩ ክሥ አሰምቷል።

በከተማዪቱ ውስጥ የአዕምሮ ጤና ችግር የነበረባቸው ጭምር የጥቃት ዒላማ መሆናቸውን ለአሜሪካ ድምፅ ሃሳባቸውን ያካፈሉ ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ይሁን እንጂ ታጣቂዎቻቸው በሲቪሎችና ሲቪል ተቋማት ላይ ጥቃት እንደማይፈፅሙ የሚናገሩት የህወሓት መሪዎች በቅርቡ ባወጡት መግለጫ ጭምር ተመሳሳይ ክሦችን ያስተባብላሉ።