የህወሃት ታጣቂዎች በአማራ ሴቶች ላይ የቡድን ጾታዊ ጥቃት መፈፀማቸውን አምነስቲ አስታወቀ

Your browser doesn’t support HTML5

ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት "አምነስቲ ኢንተርናሽናል" ዛሬ ባወጣው አዲስ ሪፖርት የህወሃት ታጣቂዎች በአማራ ክልል ተቆጣጥረውት በነበረው የነፋስ መውጫ ከተማ ሴቶችን በጠመንጃ በማስፈራራትና በቡድን መድፈራቸውን እንዲሁም ሆስፒታሎችንና የህክምና ተቋማትን መዝረፋቸውን አስታውቋል።

ጥቃት የደረሰባቸውን ሴቶች፣ ሆስፒታሎችና የሕክምና ተቋማትን ማነጋገሩን የጠቀሰው አምነስቲ ከከተማዋ አስተዳደር ያገኘው መረጃ ህወሃት ስፍራውን ለ10 ቀናት ተቆጣሮ በነበረበት በነሐሴ ወር 71 ሴቶች መደፈራቸውን እንደሚያሳይ ጠቁሞ ሁኔታው በሰብዓዊነት ላይ የደረሰጥቃት ነው ብሏል።

የአሜሪካ ድምፅ ከዚህ ቀደም በተጠቀሰው ከተማ ተገኝቶ ጥቃት የደረሰባቸውን ሴቶች ማነጋገሩ ይታወሳል። በጉዳዩ ላይ እስካሁን ከህወሃት በኩል የተባለ ነገር የለም።