በአማራ ክልል 5 ሚሊዮን ሕዝብ አስቸኳይ እርዳታ እንደሚያስፈልገው ክልሉ አስታወቀ

የአደጋ መከላከልና የምግብ ዋስትና ፕሮግራም ማስተባበሪያ ጽ/ቤት

በአማራ ክልል በወረራ ውስጥ ባሉ አራት ዞኖች የሚኖረውን ጨምሮ ከ5 ሚልዮን ህዝብ በላይ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልገው የክልሉ መንግስት አስታወቀ።

በክልሉ እስካሁን በምግብና በህክምና እጦት ሳቢያ ከ120 በላይ ሰዎች መሞታቸውን የአማራ ክልል አደጋ መከላከል ምግብ ዋስትና እና ልዩ ድጋፍ የሚሹ ኮሚሽን አስታወቀ።

በሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት ጉዳይ ዓለም አቀፍ ተቋማትን ወቅሷል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

በአማራ ክልል 5 ሚሊዮን ሕዝብ አስቸኳይ እርዳታ እንደሚያስፈልገው ክልሉ አስታወቀ