ትግራይ ውስጥ ዛሬ የአየር ጥቃት መፈፀሙን መንግሥት አስታውቋል

Your browser doesn’t support HTML5

ትግራይ ውስጥ ዛሬ የአየር ጥቃት መፈፀሙን መንግሥት አስታውቋል

ትግራይ ውስጥ ዛሬ የአየር ጥቃት ማካሄዱን የኢትዮጵያ መንግሥት አስታውቋል። ከተማዪቱን አሁን እያስተዳደሩ መሆናቸው የተነገረ ባለሥልጣን በድብደባው “የአርሶ አደሮች እህል ክምር ተቃጥሏል” ሲሉ ለቪኦኤ ገልፀዋል።

በሌላ በኩል ወደ መቀሌ ዛሬ በረራ ላይ የነበረ የእርዳታ አቅርቦት የጫነ አውሮፕላን በድብደባው ምክንያት ከአየር ላይ ዞሮ ወደ አዲስ አበባ መመለሱን የመንግሥታቱ ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ የደቡባዊና ምሥራቃዊ አፍሪካ አካባቢያዊ ቢሮ ኃላፊ ጋማ ኮኔል ዛሬ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።

መቀሌ የሚገኘው ሪፖርተራችን ሙሉጌታ አፅብሃ ያጠናቀረውና ከተለያዩ ምንጮች የደረሱን ዘገባዎች ናቸው።