ዩናይትድ ስቴትስ 453 ሺ ፀረ ኮቪድ 19 ክትባት ለኢትዮጵያ ለግሳለች

ዩናይትድ ስቴትስ ለኢትዮጵያ የለገሰችውን 453 ሺ ፀረ ኮቪድ 19 ክትባት በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ጊታ ፓሲ ለጤና ሚንስቴር አስረክበዋል። ልገሳው የተደረገው የጆ ባይደን አስተዳደር ከኮቫክስ ጋር በጥምረት ከለገሰው 25 ሚሊየን የሚጠጋ ክትባት መካከል መሆኑ ነው አምባሳደሯ ገልፀዋል ።

የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ስለክትባቱ የአሜሪካን መንግሥትን ካመሰገኑ በኋላ፤ “ኢትዮጵያ የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ለመከላከል ከፍተኛ ጥረት እያደረገች ባለበት ወቅት የተለገሰ ነው” ብለዋል።

(ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ)

Your browser doesn’t support HTML5

ዩናይትድ ስቴትስ 453 ሺ ፀረ ኮቪድ 19 ክትባት ለኢትዮጵያ ለግሳለች