መረጋጋት በሰሜን ሸዋና በኦሮምያ ዞኖች

አጣዬ

በቅርቡ በክርስትናና እስልምና እምነት ተከታዮች የተከበሩትን ኃይማኖታዊ በዓላት ሽፋን በማድረግ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋና ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞኖች ላይ ግጭት ለመቀስቀስ የተደረጉ ሙከራዎችን እንዳከሸፈ በአካባቢው የተቋቋመው የእዝ ማእከል ወይም ኮማንድ ፖስት አስታወቀ፡፡

ኮማንድ ፖስቱ ሥራውን ከጀመረ ወዲህ በአካባቢዎቹ አንጻራዊ ሰላም ቢረጋገጥም አመራሩ አጥፊዎችን አሳልፎ የመስጠት ቁርጠኝነት እንደማይስተዋልበት ተገልጿል፡፡

በመቶ ሽዎች ለሚቆጠሩ ሰዎች መፈናቀል፤ ለበርካቶች ሞትና አካል ጉዳት፣ እንዲሁም ለንብረት ውድመት ምክንያት የሆነው ግጭትና የሰላም እጦት የእዝ ማእከል ወይም ኮማንድ ፖስት መቋቋሙን ተከትሎ አንጻራዊ መሻሻል እየታየበት ነው እንደ አማራ ክልል ሰላምና ህዝብ ደህንነት ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ኃላፊ ኮማንደር መንገሻ አውራሪስ፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

መረጋጋት በሰሜን ሸዋና በኦሮምያ ዞኖች