በሶማሌ ክልል የፓርቲዎች ቅሬታ

ጂጂጋ

በሶማሌ ክልል ለ6ኛው ብሔራዊ ምርጫ ለመወዳደር የተዘጋጁ 3 ተቃዋሚ ፓርቲዎች እና የግል እጩዎች በጋራ ባወጡት መግለጫ ምርጫ ቦርድንና የክልሉን ገዢ ፓርቲ ኮንነዋል። የምርጫ ሂደቱ ለክልሉ ገዢ ፓርቲ አድሏዊ አሰራር እየተከተለ ነው ሲሉ ከሰዋል።

የክልሉ ገዢ ፓርቲ የሶማሌ ብልጽግና በበኩሉ በምርቻ አስፈጻሚዎችም ሆነ በአስተባባሪዎች ላይ ቅሬታ ካለ ከ3 ወር በፊት ጀምሮ ቅሬታ አቅርቦ መፍትሔ መጠየቅ ሲገባ የመራጮች ምዝገባ ሲጀመር መግለጫ ማውጣታቸው ምርጫውን እንሸነፋለን ከሚል ስጋት የመነጨ ሊሆን ይችላል ብሏል።

የምርጫ ቦርድ በበኩሉ ቅሬታ ያቀረቡት ፓርቲዎችን ወደአዲሰበባ ጠርቶ እያወያየ መሆኑም ተነግሯል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

በሶማሌ ክልል የፓርቲዎች ቅሬታ