የሰሜን ብሔራዊ ፓርክ ቃጠሎ ጠፋ

ፎቶ ፋይል፦ በሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ የሚገኘው የጭላዳ ዝንጅሮ

በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ ውስጥ ከትናንት በስተያ መጋቢት 11/2013 ዓ.ም ምሽት ተነስቶ የነበረው ቃጠሎ በአካባቢው ነዋሪዎችና በፓርኩ ሠራተኞች ርብርብ በቁጥጥር ሥር መዋሉን የፓርኩ የኅብረተሰብና ቱሪዝም ኃላፊ ለአሜሪካ ድምፅ ገለፁ።

የቃጠሎው መንስዔ እየተጣራ መሆኑን የአማራ ክልል ደንና ዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

የሰሜን ብሔራዊ ፓርክ ቃጠሎ ጠፋ