ሴቶች ፖለቲካዊ ምርጫዎች ላይ ትርጉም ባለው ሁኔታ እንዲወከሉ ማድረግ ያስፈልጋል

  • መለስካቸው አምሃ

ሴቶች በምርጫ ላይ የተሻለ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ይረዳል በሚል የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)  ያዘጋጀው አውደ ጥናት/ፎ ቶ ኢሰመኮ

ባለፉት ሰላሳ ዓመታት በኢትዮጵያ የሴቶችን የፖለቲካ ተሳትፎ ለማሳደግ የሕግና ፖሊሲ ማዕቀፎችእንዲኖሩ ከማዘጋጀት ጀምሮ የተሻለ ሥራ ቢከናወንም መብቶቻቸውን በተሟላ መልኩ የሚያረጋግጡሥራዎች ግን ገና ብዙ እንደሚቀራቸው በኢትዮጵጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን የሴቶችና ሕፃናትመብቶች ጉዳይ ከፍተኛ አማካሪ ዜናዊ ታደሰ ገለፁ።

ሴቶች በምርጫ ላይ የተሻለ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ይረዳል በሚል ኮሚሽኑ ባዘጋጀው አውደ ጥናት ላይ ገለፃ ያደረጉት አማካሪዋ፤ “ሴቶች ተሰሚነት እና ወሳኝነት እንዲኖራቸው የተለያዩ የሕብረተሰብክፍሎች እና የተደራጁ አካላት ኃላፊነት አለባቸው” ብለዋል። “ሴቶች ፖለቲካዊ ምርጫዎች ላይ ትርጉም ባለው ሁኔታ እንዲወከሉ ማድረግ ያስፈልጋል” ብለዋል።

(ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ)

Your browser doesn’t support HTML5

ሴቶች ፖለቲካዊ ምርጫዎች ላይ ትርጉም ባለው ሁኔታ እንዲወከሉ ማድረግ ያስፈልጋል