ህጻናትን ከብዝበዛ የታደጉት ሴት የናንሰንን ሽልማት አሸነፉ

Your browser doesn’t support HTML5

የኮሎምቢያ ህጻናት መብት ተሟጋች ሜዬርሊን ቬርጋራ ፕሬዝ፣ የዚህን ዓመት የናንሰንን የስደተኞች የላቀ ሽልማት አሸናፊ ሆነዋል፡፡ ሽልማቱ የተሰጣቸው ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ህጻናትን ከህገወጥ የሰዎች ዝውውርና ከወሲብ ብዝበዛ ጥቃት ተካልክለው በማዳን፣ ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ነው፡፡