አለም አቀፉ የፍልሰተኞች ቀን በኢትዮጵያ ተከበረ

Your browser doesn’t support HTML5

የአለም አቀፉ የፍልሰት ቀን ትላንት ተከብሮ ውሏል። በኢትዮጵያም በአለም አቀፉ የፍልሰት ድርጅት IOM አማካኝነት ለአንድ ሳምንት ስደተኞችን በሚመለከቱ በተለያዩ ዝግጅቶች ሲከበር ነበር ። በኢትዮጵያ የአለም አቀፉ የስደት ድርጅት IOM የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆኑት አቶ አለማየሁ ሰይፈስላሴ ‘በፍልሰት የተሰራች አለም በሚል መሪ ቃል’ ቀኑ ተከብሮ እንደዋለ ገልፀውልናል።