"በመላው አፍሪካ ላሉ ሕፃናት አሁንም ከፍተኛ እርዳታ ያስፈልጋል" አምበር ስታይም

Your browser doesn’t support HTML5

አምበር ስታይም የተወለደችው በጎንደር ደብረታቦር ከተማ ነው። የሶስት አመት ልጅ እያለች ከመሬት መጫወቻ መስሏት ያነሳችው ቦንብ ፈንድቶ ሁለት እጆቿን አሳጥቷታል። በዚህ ምክንያት የተለየ አርዳታ ፈላጊ ሆነች። ኢትዮጵያ በሚገኘው የክርስቲያን የህፃናት ማሳደጊያ ውስጥ ለተወሰነ ጊዜ ከኖረች በኃላ ለስራ ኢትዮጵያ ይኖሩ ከነበሩት ከአሜሪካውያኑ የማደጎ ወላጆቿ ጋር ወደ አሜሪካ መጣች።