No media source currently available
ግሬታ ፍራንቼስካ ዩሪ፣ የጣሊያንና የኢትዮጵያ ትውልድ ያላት የአካባቢ ጥበቃ እና የዱር እንስሳት ጥበቃ መብት ባለሞያ ናት። ግሬታ በተለይም የዝኆን ጥበቃ ተነሣሽነት ሥራዎች ላይ፣ ኢትዮጵያን ጨምሮ 25 የአፍሪካ ሀገራት ተሳታፊ በኾኑበት ተቋም አማካኝነት ብዙ ሥራዎችን ሠርታለች። በአሁን ሰዓት፣ አፍሪካውያን ሴቶች በአካባቢ ጥበቃ ሥራዎች ላይ እንዲሳተፉ በሚቀሰቅስ 'ሴቶች ለአካባቢ ጥበቃ' የተባለ ድርጅት መሥራች እና ባልደረባ ናት።
ስለ ሥራዋ እና የዱር እንስሳት ጥበቃ እንቅስቃሴዎቿ በተመለከተ ከአሜሪካ ድምፅ ጋራ ያደረገችውን ቆይታ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።