በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የአሜሪካ ቀጣሪዎች  በሃያዎቹ ዕድሜ ውስጥ ያሉ ወጣቶችን መቅጠር አይፈልጉም ተባለ 


የአሜሪካ ቀጣሪዎች  በሃያዎቹ ዕድሜ ውስጥ ያሉ ወጣቶችን መቅጠር አይፈልጉም ተባለ 
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:00 0:00

ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ የተሰራ አንድ አዲስ ጥናት 40 በመቶ የሚሆኑ ስራ ቀጣሪዎች እድሜያቸው በ20ዎቹ የሚገኙ ወጣቶችን ለመቅጠር እንደማይሹ ጠቆመ። በቅርቡ ይፋ የተደረገው ይኸው ጥናት አብዛኞቹ ቀጣሪዎች እድሜያቸው  በአስራዎቹ ማብቂያ እና በሃያዎቹ ውስጥ የሚገኙ  በምህጻር ‘ጄን ዚ’  የሚባሉትን አዲስ ተመራቂ  ወጣቶችን ለመቅጠር ፍቃደኛ እንዳልሆኑ ነው ያመላከተው። 

ጥናቱ 800 የሚሆኑ የድርጅቶች ስራ አስኪያጆች እና ዋና ስራ አስፈጻሚዎች ላይ የተደረገ ሲሆን፤ ከ 10 ቀጣሪዎች መካከል አራቱ የቅርብ ጊዜ ተመራቂዎች “ሃላፊነት የማይሰማቸው እና ለስራ ብቁ አይደሉም" ብለው ስለሚያምኑ እንደማይቀጥሯቸው ተገልጿል። ኤደን ገረመው የዶራ ሜካወርን ዘገባ እንደሚከተለው አሰናድታዋለች።

XS
SM
MD
LG