በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አሜሪካ ለአስቸኳይ ጊዜ የምግብ እርዳታ የሚውል ተጨማሪ የ35 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ይፋ አደረገች


የዩናይትድ ስቴትስ ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (United States Agency for International Development/USAID)
የዩናይትድ ስቴትስ ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (United States Agency for International Development/USAID)

ዩናይትድ ስቴትስ የአስቸኳይ ጊዜ የምግብ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ኢትዮጵያዊያን የሚሆን የ35 ሚሊዮን ዶላር ተጨማሪ ድጋፍ ዛሬ ይፋ አድርጋለች።

ዩናይትስ ስቴትስ ዛሬ ይፋ ያደረገቸው ተጨማሪ ድጋፍ የበልጉን ግምገማ ተከትሎ የተከለሰው የሰብዓዊ እርዳታ ሰነድ ይፋ ከተደረገ በኃላ የመጀመርያው ነው።

ይህንኑ ሰነድ ባለፈው ሳምንት ይፋ ያደረጉት መንግሥትና አጋሮቹ 10.2 ሚሊዮን የነበሩት የተረጂዎች ቁጥር ወደ 9.7 ሚሊዮን ዝቅ ማለቱን ጠቁመዋል።የነዚህን ተረጂዎች ፍላጎት እስከ መጪው ታህሳስ ወር ለሟሟላት የ600 ሚሊዮን ዶላር ተጨማሪ ገንዘብ እንደሚያስፈልግ ጠቅሰዋል።

ዛሬ ይፋ የተደረገው የዩናይትድ ስቴትስ ድጋፍ ይሄንኑ የሚያግዝ ነው።ድጋፉን ይፋ ያደረጉት በኢትዮጵያ የዩስኤድኣይዲ ዳይሬክተር ለስሊ ሪድ ናቸው።

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

አሜሪካ ለአስቸኳይ ጊዜ የምግብ እርዳታ የሚውል ተጨማሪ የ35 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ይፋ አደረገች
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:15 0:00

XS
SM
MD
LG