No media source currently available
የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዘዳንት ጆ ባይደን “የሩሲያ ወታደሮች የሚያደርጉት ማንኛውም ዓይነት ወደ ዩክሬን ዘልቆ የመግባት እንቅስቃሴ ሁሉ እንደ ወረራ ይቆጠራል” ካሉ በኋላ ዩናይድ ስቴትስ ወደ ዩክሬን አደገኛ የሆኑ የጦር መሳሪያዎች ድጋፍ መላክ ጀምራለች፡፡ በተመሳሳይ የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃልኪዳን ድርጅት የሆነው የኔቶ አባል ሃገራትም ወደ ዩክሬን መሳሪያ መላክ ጀምረዋል፡፡