በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ድርቅ የጎዳው ሶማሌ ክልል


ድርቅ የጎዳው ሶማሌ ክልል
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:47 0:00

በሶማሌ ክልል በቀጠለው ድርቅ ምክኒያት የእንስሳት ሞት መጨመሩን ክልሉ አስታወቀ። አንዳንድ አካባቢዎች የበልግ ዝናብ ቢያገኙም ለአራተኛ ዓመት የቀጠለው የድርቅ ሁኔታ ባለመቀረፉ በተለይም በሦስት ዞኖች እንስሳት እየሞቱ መሆኑን ጨምሮ ገልጿል።

ድርቁ ከበረታባቸው ዞኖች አንዱ በሆነው ዳዋ ዞን ብቻ ከአንድ ሺህ በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውና ከ300ሺ በላይ የቁም እንስሳት መሞታቸውን ክልሉ አስታውቋል።

የዳዋ ዞን ነዋሪዎች ከችግሩ ስፋት አንጻር በቂ ድጋፍ እየተደረገላቸው እንዳልሆነ ጠቁመዋል። የሚችሉትን ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን የገለጸው የሶማሌ ክልል አቅም ያላቸው ሁሉ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል።

XS
SM
MD
LG