በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የአማራ ክልል ልዩ ኃይሎች ከትግራይ ለቀው ወጡ


የአማራ ክልል ልዩ ኃይሎች ከትግራይ ለቀው ወጡ
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:46 0:00

ከኢትዮጵያ ጦር ጎን ተሰልፈው ከትግራይ ተዋጊዎች ጋር ሲዋጉ የነበሩት የአማራ ክልል ልይ ኃይሎች በኅዳር ወር በተደረሰው የሰላም ስምምነት መሰረት ከሽሬ እና አካባቢው ለቀው መውጣታቸውን የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አስታወቀ።

መከላከያ ሰራዊቱ ዛሬ ሐሙስ ባወጣው መግለጫ የአማራ ክልል ኃይሎች ከተባሉት አካባቢዎች ለቀው እንዲወጡ መታዘዛቸውን ያስታወቀ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጀነራል አበባው ታደሰ የክልሉ ኃይል ሲወጣ መመልከታቸውን ተናግረዋል።
በአክሱምና ሽሬ መካከል በምትገኘው ሰለኽለኻ በተባለች አካባቢ እንደሚኖሩ በስልክ የነገሩን አንድ ስማቸው እንዲጠቅ ያልፈለጉ የአካባቢው ነዋሪ ከአራት ቀናት በፊት ቁጥራቸው የበዛ አውቶብሶች የታጠቁ ኃይሎች ይዘው ከከተማው ሲወጡ መመልከታቸውን ገልፀውልናል።

ሆኖም ከትግራይ ባለስልጣናት እስካሁን የተሰጠ አስተያየት የለም።

XS
SM
MD
LG