በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ የኢትዮጵያ ጉብኝት


የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ የኢትዮጵያ ጉብኝት
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:04 0:00

የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ዛሬ በኢትዮጵያ ባደረጉት የአንድ ቀን የሥራ ጉብኝት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር ተወያይተዋል።

ፕሬዚዳንት ሩቶ በትዊተር ገጻቸው “ውይይቱ የሁለቱ ሀገራት የድንበር ተሻጋሪ ንግድ ማሳደግ ላይ ያተኮረ ነበር” ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ የላሙን ወደብ ለደቡቡ የኢትዮጵያ ክፍል እንደ መነሻ ወደብ እንድትጠቀም ፕሬዚዳንቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይን መጠየቃቸውንም ጽ/ቤታቸው ገልጿል፡፡

አዲሱ የኬንያ ፕሬዚዳንት ሩቶ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጋር ሆነው፣ በቅርቡ በኢትዮጵያ የስልክ አገልግሎት መስጠት የጀመረውን የኬንያውን ሳፋሪኮም ኩባንያ ሥራ በይፋ ማስጀመራቸውንም በትዊተር ገፃቸው አስታውቀዋል፡፡

ፕሬዚዳንቱ በኢትዮጵያ ያደረጉትን የአንድ ቀን ጉብኝት አጠናቅቀው ዛሬ አመሻሽ ላይ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡

XS
SM
MD
LG