በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አማራ ክልል ጀውሃና ሰንበቴ ላይ ግጭት አለ



አማራ ክልል ጀውሃና ሰንበቴ ላይ ግጭት አለ
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:30 0:00

በአማራ ክልል በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ሰንበቴ ከተማና አካባቢው ዛሬ በመሣሪያ የታገዘ ግጭት እንደነበረ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አህመድ አሊ ለአሜሪካ ድምፅ ገልፀዋል።

ከትናንት በስትያም ሰሜን ሸዋ ዞን ውስጥ ጀውሃ ላይ ሌላ ግጭት እንደነበረ ተሰምቷል።

የሰንበቴው ግጭት የተቀሰቀሰው የጀውሃውን ሁኔታ ለመቆጣጠር ጥረት እየተደረገ ባለበት ወቅት መሆኑን ያመለከቱት አቶ አህመድ አሊ መንስኤውንና የደረሰውን ጉዳት አስመልክቶ መረጃ እንደሌላቸው ተናግረዋል።

የአማራ ክልል መንግሥት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ ግዛቸው ሙሉነህ በጉዳዩ ላይ የክልሉ መንግሥት እየተነጋገረ መሆኑን አመልክተዋል።

ለዝርዝሩ ዘገባውን የያዘውን ፋይል ይመልከቱ።

XS
SM
MD
LG