በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ሰማያዊ ፓርቲ ለአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር የለውጥ ጥሪ አቀረበ፤ በጀትና ዕቅዱንም አወጣ


ኢትዮጵያ
ኢትዮጵያ

አዲሱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ "አፋኝ" በሆኑ ሕጎች ላይ መሠረታዊ ማስተካከያ ለማድረግ እንዲሠሩ ሰማያዊ ፓርቲ ጥሪ አቅርቧል፤ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች አንፃር "ከፍተኛ" የተባለ የዓመት በጀት መመደቡንም አስታወቀ፡፡



please wait

No media source currently available

0:00 0:05:09 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

please wait

No media source currently available

0:00 0:09:07 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ


በሃገሪቱ ፓርላማ ሲፀድቁ የተቃዋሚዎችን ይሁንታ ያላገኙት አንዳንድ ሕጎች ዛሬም የልዩነት ነጥቦች ሆነው ቆይተዋል፡፡
ፀረ-ሽብር ሕጉ፣ የሲቪክ ማኅበራት ማደራጃና የመሣሰሉት ከእነዚህ ሕጎች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው፡፡
በአብዛኛው በአንድነት ፓርቲ ውስጥ በተፈጠረው ልዩነት በራሣቸው መንገድ መጓዝን በመረጡ አባላት በቅርቡ የተቋቋመው ሰማያዊ ፓርቲ እነዚህን የመሣሰሉ ሕጎች ባሉበት ሊቀጥሉ እንደማይገባ አመልክቷል፡፡
በአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ የሚመራው መንግሥት የማስተካከያ እርምጃ እንዲወስድ ጠይቋል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች አንፃር ከፍተኛ የተባለ ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ለአንድ ዓመት መድቦና የሥራ ዕቅድ አዘጋጅቶ ትግሉን ለመምራት መዘጋጀቱን ፓርቲው አስታውቋል።
የተጠቀሰውን ያህል ገንዘብ ማሰባሰብ "በእርግጥም የሚቻል ነው" ሲሉ የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ ይልቃል ጌትነት ለቪኦኤ ገልፀዋል።
እንዴት?

የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ ይልቃል ጌትነት ከቪኦኤ ጋር ተነጋግረዋል፡፡

የእስክንድር ፍሬውን ዘገባዎች ያዳምጡ፡፡
XS
SM
MD
LG