በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ከኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት ጋራ ይጀመራል የተባለው ድርድር ተስፋ እንደፈነጠቀላቸው ነዋሪዎች ተናገሩ


ከኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት ጋራ ይጀመራል የተባለው ድርድር ተስፋ እንደፈነጠቀላቸው ነዋሪዎች ተናገሩ
please wait

No media source currently available

0:00 0:08:48 0:00

በኢትዮጵያ መንግሥት እና በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት መካከል ነገ በታንዛኒያ ይጀመራል የተባለው ድርድር የሰላም ተስፋ እንደፈነጠቀላቸው ሁለቱ አካላት በሚዋጉባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ነዋሪዎች ገለጹ።

ግጭት ካለባቸው የኦሮሚያ ክልል አካባቢዎች ለአሜሪካ ድምፅ አስተያየታቸውን የሰጡት ነዋሪዎች፣ ድርድሩ ለዓመታት የዘለቀውን አለመረጋጋት ሊያስወግድ ይችላል በሚል ተስፋ መደሰታቸውንም ተናግረዋል፡፡ ሁለቱም አካላት ሕዝቡን ተሳቢ በማድረግ በቅንነት እንዲደራደሩም ጠይቀዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒሰትር ዐቢይ አህመድ በሁለቱ ወገኖች መካከል ነገ ድርድር እንደሚጀመር ትላንት ይፋ ያደረጉ ሲሆንየኦሮሞ ነጻነት ሠራዊትም የሠላም ውይይቱ በሦስተኛ ወገን አደራዳሪነት እንደሚካሄድ አረጋግጧል።

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

XS
SM
MD
LG