በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የቃፍታ ሸራሮ ብሔራዊ ፓርክ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት ተገለፀ


የቃፍታ ሸራሮ ብሔራዊ ፓርክ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት ተገለፀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:56 0:00

የቃፍታ ሸራሮ ብሔራዊ ፓርክ በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ፡፡ ብሔራዊ ፓርኩ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ በአጋዘን ሀብት ሁለተኛ የነበረ ሲሆን፣ ጦርነቱን ተከትሎ በተስፋፋ ሕገወጥ አደን ምክንያት በአሁኑ ጊዜ ግን አጋዘን ማየት ወደማያልበት ሁኔታ መደረሱን የፓርኩ ተወካይ ኃላፊ ለቪኦኤ ተናግረዋል፡፡

በግጭትና በጦርነት ወቅት ብሔራዊ ፓርኮች የተለያዩ ችግሮች ሰለባ እንደሚሆኑ ቪኦኤ ያነጋገራቸው አንድ የተፈጥሮ ሀብት ተመራማሪ ገልፀዋል፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ለተፈጥሮ ሀብቶች የአደጋ መከላከል ዕቅድ ስለማይኖር አለመረጋጋቶች ሲከሰቱ ፓርኮች በቀላሉ ለጥቃት እንደሚጋለጡ አስረድተዋል፡፡

XS
SM
MD
LG