No media source currently available
የተባበሩት መንግሥታት የሥደተኞች ጉዳይ ኮሚሽን /ዩኤንኤችሲአር/ ኬንያ የነበሩ የኢትዮጵያ ስደተኞችን ወደ ሀገር መመለሱን አስታወቀ። የዩኔንኤችሲአር ቃልአቀባይ ድርጅታቸው በመጭው ወራት በፈቃደኝነት ወደ ሀገር ለመግባት የተመዘገቡ ስደተኞችን ይመልሳል ብሏል።