No media source currently available
ህወሓት ትናንት ሌሊት ወደ ባህርዳር የተኮሳቸው ሮኬቶች ምንም ዓይነት ጉዳት አለማድረሳቸውን የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሜጄር ጄነራል ይልማ መርዳሳ አስታወቁ። ሮኬቶቹ ከየት እንደተተኮሱ እናውቃለን ያሉት ዋና አዛዡ ያረፉትም በገበሬ ማሳ ላይ ነው ሲሉ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።