No media source currently available
ለሦስት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ኢትዮጵያ የገቡት የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሣያስ አፈወርቂ በዛሬው ውሏቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር በጅማ የቡና እርሻ ውስጥ ውለዋል። የኤርትራው ፕሬዚዳንት የቡና ግብርናን በሃገራቸው ለማላመድ ያላቸውን ፍላጎት ገልፀዋል። ጅማ ዩኒቨርስቲንም ጎብኝተዋል።