በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የዘይት ወረፋ - ድሬዳዋ


የዘይት ወረፋ - ድሬዳዋ
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:16 0:00

ዛሬ ድሬዳዋ ላይ የታየው በአንድ ሊትር 48 ብር የሚያወጣውን ዘይት ከነጋዴዎች ከመግዛት በመንግሥት ሊትሩ በ26 ብር ሂሳብ የሚቀርበውን ዘይት ለመግዛት የተያዘ ወረፋ ነው፡፡ ቀኑን ሙሉ ወረፋ ይዘው ሳይደርሳቸው ለነገ የተቀጠሩም አሉ፡፡ ለአንድ ቤተሰብ በሽያጭ የሚቀርበው ከፍተኛው መጠን 5 ሊትር ነው፡፡

ኢትዮጵያ /SNV/ በተባለው ግብረሰናይ ድርጅት መረጃ መሰረት በ2005 ላይ 50 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን የነበረው ዓመታዊ የምግብ ዘይት ግዢ በፍጥነት አድጎ 15 ዓመት ባልሞላ ጊዜ ወስጥ ነው 400 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ደርሷል፡፡
በሌላ በኩል ባሰሳለፍነው የበጀት ዓመት 350ሺ ቶን ገደማ ሰሊጥ ወደውጭ ተልኮ 500 ሚሊዮን ዶላር ገደማ የውጭ ምንዛሬ መገኘቱን የግብርናና ተፈጥሮ ሃብት ሚኒስቴር አምና ይፋ ያደረገው መረጃ ያመለክታል፡፡ ሃገረቱ ግን ከዚህ ከዕጥፍ በላይ ሰሊጥ የማምረት አቅም ሁሉ አላት፡፡ ሆኖም በዘርፉ ላይ የሃገር ውስጥ የዘይት ገበያን ለመሸፈን የሚያስችል በቂ ሥራ ባለመሰራቱ ሃገሪቱ ባለፉት ዓመታት ሰሊጥ እየሸጠች ዘይት እየገዛች ትገኛለች፤ የዘይት አቅርቦቱም ወጥነት የሌለው በመሆኑ ዕጥረት እና የዋጋ መናር የሚስተዋልበት ነው፡፡

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG