በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በቦረና እና ጉጂ በድርቅ የተነሣ ሰው እንደ በሬ ተጠምዶ እያረሰ መኾኑን አርሶ አደሮች ገለጹ


በቦረና እና ጉጂ በድርቅ የተነሣ ሰው እንደ በሬ ተጠምዶ እያረሰ መኾኑን አርሶ አደሮች ገለጹ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:28 0:00
ከአምስት ተከታታይ የዝናም ወቅቶች መታጎል በኋላ፣ በደቡብ ኦሮሚያ ዝናም ቢዘንምም፣ አሁንም አርሶ አደሮቹ፥ በዘር፣ በማዳበርያ እና በማረሻ በሬ ማጣት ችግር ላይ እንደ ኾኑ ተናግረዋል።
በቦረና ዞን አንድ የድሬ ወረዳ አርሶ አደር፣ ያለፈው ድርቅ በርካታ የቁም ከብቶችን ስለ ፈጀ፣ አሁን ነዋሪው የሚያርስበት ከብት አጥቶ፣ ሰውን ልክ እንደ በሬ በመጥመድ የተገኘውን የእህል ዘር ለመዝራት እየሞከሩ መኾናቸውን ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።
በጉጂም በተመሳሳይ፣ የዘር እና የማዳበሪያ አለመኖር ብቻ ሳይኾን፣ በአካባቢው ያለው የጸጥታ ዕጦት፣ የአርሶ አደሮቹን ችግር ማባባሱን ነዋሪዎች ገልጸዋል።
የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ፣ አርሶ አደሮቹ፣ የእርሻ ግብአቶቹን እንዲያገኙ እየሠራኹ ነው፤ ይላል።
XS
SM
MD
LG