በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ለቤኒሻንጉል ክልል መልሶ መቋቋም ከ38 ቢሊዮን ብር በላይ ያስፈልጋል ተባለ


ለቤኒሻንጉል ክልል መልሶ መቋቋም ከ38 ቢሊዮን ብር በላይ ያስፈልጋል ተባለ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:19 0:00

ባለፉት ሁለት ዓመታት ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውስጥ በነበረው የፀጥታ ችግር የደረሰውን ጉዳት ለመቀልበስና እና መልሶ ለማቋቋም ከ38 ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚያስፈልግ የክልሉ መንግሥት ገለጸ።

የክልሉ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ታረቀኝ ታሲሳ "በሦስት ዞኖችና አንድ ልዩ ወረዳ ውስጥ የወደሙ የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን መልሶ ለመገንባትና ለማደስ ከሁለት እስከ አምስት ዓመት ይወስዳል" ካሉ በኋላ ለተግባራዊነቱም ኅብረተሰቡ፣ መንግሥትና የተለየዩ የግብረ ሠናይ ድርጅቶች በጋራ እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።

ከክልሉ ተፈናቅለው ከነበሩ 475 ሺ ሰዎች መካከል እስከ አሁን ከ265 ሺ በላይ የሚሆኑ ወደየአካባቢያቸው መመለሳቸውን ኃላፊው ጨምረው ገልጸዋል።

በክልሉ የሚንቀሳቀሰው "ቦሮ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ" የተባለው ተፎካካሪ የፖለቲካ ድርጅት "በክልሉ ግጭት በነበረባቸው አካባቢዎች ለደረሰው ጉዳት የተሰጠው ትኩረት፣ አናሳ ነው" ሲል አስታውቋል።

XS
SM
MD
LG