በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የባልደራስ የቀድሞው መሪ እስክንድር ነጋ ከእስር መለቀቅ


የባልደራስ የቀድሞው መሪ እስክንድር ነጋ ከእስር መለቀቅ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:37 0:00

በቅርቡ ራሳቸውን ከፖለቲካ ማግለላቸውን የገለጹት አቶ እስክንድር ነጋ ከሁለት ቀናት እስር በኋላ በትናንትናው ዕለት ተለቀዋል።

የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ መስራች እና የፓርቲው ፕሬዝዳንት የነበሩት አቶ እስክንድር ነጋ የካቲት 17/2015 ዓ.ም አመሻሽ ላይ በምዕራብ ጎጃም ዞን ቡሬ ወረዳ አካባቢ በፀጥታ ኃይሎች ተይዘው ከቆዩ በኋላ ትላንት መለቀቃቸውን ፓርቲው አስታውቋል፡፡

ጉዳዩን በተመለከተ አስተያየታቸውን የጠየቅናቸው የፓርቲው ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ቀለብ የቀድሞው የባልደራስ መሪ “በቁጥጥር ስር የዋሉት ምንም አይነት የእስር ማዘዣ ሳይወጣባቸው እና የተለቀቁትም ለፍርድም ሳይቀርቡ ነው” ያሉት ወ/ሮ ቀለብ፣ ተጨማሪ አስተያየት ከመስጠት ግን ተቆጥበዋል፡፡

ስለ አቶ እስክንድር እስርም ሆነ ከእስር የመለቀቃቸው ጉዳይ በመንግሥት በኩል እስካሁን የተባለ ነገር የለም፡፡

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ፡፡

XS
SM
MD
LG