በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የጀውሃ አካባቢው ግጭት ውሎ


የጀውሃ አካባቢው ግጭት ውሎ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:01 0:00

ባለፈው ቅዳሜ ጥር 13 በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጀውሃ አካባቢ በተቀሰቀሰው ግጭት ከሰሜን ሸዋም ከኦሮሞ ብሔረሰብ ዞንም ብዙ ህይወት መጥፋቱና ሰፊ ጉዳት መድረሱ ተገልጿል።

የክልሉ መንግሥት ዛሬ ባወጣው መግለጫ ‘ፀረ ሰላም’ ሲል የጠራቸው ታጣቂዎች ‘በክልሉ ልዩ ኃይልና ፌደራል ፖሊስ ላይ ጥቃት ፈፅመው ጉዳት አድርሰዋል’ ብሏል።

መግለጫው ጥቃት አድራሾቹ በሰሜን ሸዋ ዞንና በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን አዋሳኝ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ውስጥ በሚኖሩ “ሰላማዊ ሰዎች ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን” አመልክቷል።

በከባድ መሳሪያ የታገዘ ነው በተባለው ጥቃት የንብረት ጉዳትም መድረሱን ከአካባቢዎቹ የሚወጡ መረጃዎች ጠቁመዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

XS
SM
MD
LG