በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በሶማሊያዎቹ ሁለት የአጥፍቶ ጠፊ ቦምብ ፍንዳታ 15 ሰው ተገደለ


በሶማሊያዎቹ ሁለት የአጥፍቶ ጠፊ ቦምብ ፍንዳታ 15 ሰው ተገደለ
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:21 0:00

የሶማሊያ ባለሥልጣና ትናንት ረቡዕ በማዕከላዊ ኺራን ክፍለ ግዛት በደረሱ ሁለት የቦንብ ፍንዳታዎች በትንሹ 15 ሰው መሞቱን አስታውቀዋል።

ጥንዶቹ የአጥፍቶ ጠፊ ጥቃቶች የደረሱት ማኻስ በተባለቸው ከተማ ትናንት ረቡዕ ማለዳው ላይ ነው። በኺራን ክፍለ ግዛት ውስጥ ያለችው መኻስ ከተማ የምትገኘው ከሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃድሾ በስተስሜን 300 ኪሎ ሜትሮች ርቀት ላይ ነው።

በመንግሥት ቴሌዥን ስለጥቃቱ መግለጫ የሰጡት የከተማይቱ ከንቲባ ሙኒ መሀመድ ሃለኔ ተሸከርካሪ ላይ የተጠመዱት ሁለቱ የቦምብ ጥቃቶች በመኖሪያ ቤታቸው ላይ እና በፌዴራሉ መንግሥት፣ የምክር ቤት አባል መኖሪያ ቤት ላይ የተነጣጠሩ መሆኑን ተናግረዋል።

በጥቃቱም በርካታ ጉዳቶች መድረሳቸውን ገልጸዋል፡፡

XS
SM
MD
LG