በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኢትዮጵያ ለኬንያ ከምትሸጠው የኤሌክትሪክ ኃይል 100 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት አቅዳለች


ኢትዮጵያ ለኬንያ ከምትሸጠው የኤሌክትሪክ ኃይል 100 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት አቅዳለች
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:04 0:00

ኢትዮጵያ ለኬንያ ከምትሸጠው የኤሌክትሪክ ኃይል በዓመት 100 ሚሊዮን ዶላር ገቢ እንደምታገኝ ተገለፀ። ሽያጩ ባለፈው ሐሙስኅዳር 8/ 2015 ዓ.ም 75 ሜጋዋት ኃይል በመላክ መጀመሩን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮምዩኒኬሽንስ ዳይሬክተር አቶ ሞገስመኮንን ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡ ሽያጩም በሦስት ዓመት ውስጥ ወደ 200 ሜጋ ዋት እንደሚያድግ አመልክተዋል፡፡

የመሸጫ ዋጋው በኪሎ ዋት በሰዓት 65 የአሜሪካ ሳንቲም እንደሆነ አቶ ሞገስ ገልፀዋል። የኬንያ የኃይልና የነዳጅ ተቆጣጣሪ ባለሥልጣንም የኃይል ንግድ ሥምምነቱ ለመነሻነት በ75 ሜጋዋት ይፋ መደረጉን ገልፆ፣ መደበኛው የኃይል ንግድግን በ150 ሜጋ ዋት እንደሚጀመር አስታውቋል፡፡

XS
SM
MD
LG