በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ፖሊስ ሸኔ እና ጽንፈኛ ፋኖ በሚል የሚገልጻቸው ቡድን አባላት ማሰሩን አስታወቀ


ፖሊስ ሸኔ እና ጽንፈኛ ፋኖ በሚል የሚገልጻቸው ቡድን አባላት ማሰሩን አስታወቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:33 0:00

በአዲስ አበባ ከተማና ዙሪያው “ሽብር፣ ሁከትና ብጥብጥ ለመፍጠር ሲንቀሳቀሱ ነበር” ያላቸውን 371 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ-ኃይል አስታወቀ። በቁጥጥር ስር ከዋሉት መካከል ከ200 በላይ የሚሆኑት መንግሥት አሸባሪ ብሎ የፈረጀው የሸኔ እና ጽንፈኛ በሚል የሚገልጻቸው የፋኖ ቡድን አባላት ስለመሆናቸው ግብረ ኃይሉ አመልክቷል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ መንግሥት ሸኔ ብሎ ከሚጠራው እና ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ከሚለው ቡድንም ይሁን የፋኖ ወኪል ነኝ ከሚል አካል በይፋ የተሰጠ ምላሽ የለም፡፡

የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ-ኃይሉን መግለጫ በተመለከተ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ጄላን አብዲን አነጋግረናቸዋል።

XS
SM
MD
LG